/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ 21 ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ሐምሌ 16/2014 ዓ.ም. የተማሪዎች የምረቃ በዓል አከናውኗል፡፡የኮሌጁ መመህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ነው የምርቃት ስነስርአቱ የተካሄደው፡፡ የኮሌጁ ምክትል ዲን መምህር ሔኖክ ዲታ ባደረጉት ንግግር በመከላከል ላይ የተመሠረተውን የሀገራችን የጤና ፖሊሲ ከመተግበር አንጻር ኮሌጁ ለሀገራችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን መሆኑን ገልጸዋል።

 

ኮሌጁ በ2014 ዓ.ም በነርሲንግ ፣ በፋርማሲ ፣ በሚድዋይፍ ፣ በላብራቶሪ ፣ በኢንቫይሮመንታል ኸልዝ ፣ በጀነሪክና አፕግሬድ ጤና ኤክስቴንሽን እና በአንስቴዥያ ሙያ በመደበኛ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 726 የጤና ባለሙያዎች አስመርቋል።

የደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

የደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ግንቦት 15/2013 ዓ.ም. የተማሪዎች የምረቃ በዓል አከናውኗል፡፡የኮሌጁ መመህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ነው የምርቃት ስነስርአቱ የተካሄደው፡፡  የኮሌጁ ዲን አቶ ማሙዬ መንገሻ ባደረጉት ንግግር ትምህርት የአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እድገት ለማምጣት የሚረዳ ቁልፍ መሣሪያ በመሆኑ ኮሌጃችንም ይህንን በመረዳት ጥራት ያለው፣ደረጃውን የጠበቀና ውጤት ሊያመጣ የሚችል ሥልጠና በመስጠት ብቃት ያላቸው ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎችን ለማፋራት አላማዬ ብሎ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡

የደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ቀደም ሲል በመለስተኛ ጤና ባለሙያዎች ማሠልጠኛ ት/ቤትነት በ1991 ዓ.ም የተመሠረተ ሲሆን በ1997 ዓ.ም ከክልሉ መንግስትና ከጤና ጥበቃ ቢሮ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ወደ ጤና ኮሌጅነት ያደገ ኮሌጅ ነው፡፡

ኮሌጁ ማህበረሰብ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ

የክልሉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት በማሟላት በጤናው ዙሪያ አኩሪ ተግባር እየፈፀመ ያለው ኮሌጃችን አሁንም የት/ት ስትራቴጂውን በመቀየስ ይህንኑ ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ለዚህም የትምህርት ጥራትን አስጠብቆ በቂ ልምድና እውቀትን ማዳበር አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል፡፡ ለዚህ ነው እንግዲህ የደ/ብርሃን ጤና ሳይንስ ኮሌጅም ለመምህራኑ እና ለሠራተኞቹ የተለያዩ የአቅም መገንቢያ ስልጠናዎችን ከተለያዩ አካላት ጋር በመገናኘት አጫጭር ስልጠናዎችን በበጀት አመቱ የሰጠው ለዚህም ተግባር

የኮሮና ቫይረስ (COVID 19) ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች  

በዓለማችን ብሎም በሀገራችን ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ ችግር እያስከተለና እየተስፋፋ የመጣውን ኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብሎ ደ/ብርሃን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተለያዩ  ስራዎችን በመስራት ላይ ነው ያሉት የደብረብርሃን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ  ዲን አቶ ማሙዬ መንገሻ፤

  • ቫይረሱን የመከላከል ሥራን በተመለከተ የኮሌጁን ባለሙያዎችን በማቀናጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ በሞንታርቦ ፣ በበራሪ ወረቀቶች አባዝቶ በመስጠት፣ፖስተር እና ባነር በማዘጋጀት ለአካባቢውና ለዞኑን ማህበረሰብ የተሰራ ሲሆን በቀጣይም በተከታታይ የምንሰራው ነው ብለዋል፣

Page 1 of 2

Federal Ministry of Health

የፌደራል ጤና ጥበቃ ቢሮ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና የሕብረተሰቡን የጤና ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል ከ21 ጤና ሣይንስ ኮሌጆች ጋር በቅንጅት በመስራት ብቁ የጤና ባለሙያዎችን እንዲያፈሩ፤ ለህብረተሰቡ ችግር ፊቺ የሆኑ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ በተለያየ መልኩ ድጋፍ በማድረግና በቅንጅት በመስራት ሀገራዊ የጤና ተልእኮን ለማሳካት ከጤና ሣይንስ ኮሌጆች ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ more...

Amhara regional health bureau

የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና የሕብረተሰቡን  የጤና ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል ረገድ ከጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር በቅንጅት በመስራት ርህሩህ፣ተገልጋይ አክባሪ እና ሙያዊ ስነ ምግባር የተላበሱ የጤና አገልግሎት ሰጪዎች የማፍራት ስራ፤ ለህብረተሰቡ ችግር ፊቺ የሆኑ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ የጤና አገልግሎት በመስጠት ከጤና ኮሌጁ ጋር በቅንጅት በመስራት ሀገራዊ የጤና ተልእኮን ለማሳካት በጋራ ከጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ more...