/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ 21 ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ሐምሌ 16/2014 ዓ.ም. የተማሪዎች የምረቃ በዓል አከናውኗል፡፡የኮሌጁ መመህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ነው የምርቃት ስነስርአቱ የተካሄደው፡፡ የኮሌጁ ምክትል ዲን መምህር ሔኖክ ዲታ ባደረጉት ንግግር በመከላከል ላይ የተመሠረተውን የሀገራችን የጤና ፖሊሲ ከመተግበር አንጻር ኮሌጁ ለሀገራችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን መሆኑን ገልጸዋል።

 

ኮሌጁ በ2014 ዓ.ም በነርሲንግ ፣ በፋርማሲ ፣ በሚድዋይፍ ፣ በላብራቶሪ ፣ በኢንቫይሮመንታል ኸልዝ ፣ በጀነሪክና አፕግሬድ ጤና ኤክስቴንሽን እና በአንስቴዥያ ሙያ በመደበኛ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 726 የጤና ባለሙያዎች አስመርቋል።

ከነዚህ ተመራቂዎች ውስጥ 90 በመቶ ሴቶች መሆናቸውንና የዛሬዎቹን ሳይጨምር ከዚህ በፊት በተለያዩ ዙሮች 5 ሺህ 728 ተማሪዎች በማሰለጠን ለሥራ አሰማርቷል ሲሉ የኮሌጁ ምክትል ዲን መምህር ሔኖክ ዲታ ተናግረዋል።


የዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት የሰሜን ሸዋ ዞን ምክትል ጤና መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ፀዳለ ሰሙንጉሥ እንደተናገሩት የጤናው ሴክተር መከላከልን መሠረት ያደረገ ፓኬጅ በመተግበር ሞዴል የሆኑ የጤና ተቋማትና በመገንባትና የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በማሰማራት ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም እናቶች ከቅድመ ወሊድ ጀምሮ በጤና ተቋማት እንድወልዱ በማድረግ በወሊድና ተያያዥ ምክንያቶች እንዳይሞቱ በማድረግ የእናቶችንና ሕጻናትን ሞት በመቀነስ የድርሻውን እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን የዛሬ ተመራቂዎችም ለጤናው ዘርፍ ተጨማሪ አቅም ናችሁ ሲሉ የክብር እንግዳዋ ተናግረዋል።

ተመራቂዎች ከኮሌጁ በትምህርት ያገኛችሁትን ዕውቀት ከምርቃት በኋላ በተከበረው የጤና ሙያ ወደሥራ ስትሰማሩ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ዘር ፣ ብሔርና ቀለም ሳትለዩ ርኅራኄና ትህትና የተሞላበት አገልግሎት በመስጠት የገባችሁትን ቃለ መሐላ ተግባራዊ ማድረግ አለባችሁ በማለት ወይዘሮ ፀዳለ አሳስበዋል።

Federal Ministry of Health

የፌደራል ጤና ጥበቃ ቢሮ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና የሕብረተሰቡን የጤና ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል ከ21 ጤና ሣይንስ ኮሌጆች ጋር በቅንጅት በመስራት ብቁ የጤና ባለሙያዎችን እንዲያፈሩ፤ ለህብረተሰቡ ችግር ፊቺ የሆኑ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ በተለያየ መልኩ ድጋፍ በማድረግና በቅንጅት በመስራት ሀገራዊ የጤና ተልእኮን ለማሳካት ከጤና ሣይንስ ኮሌጆች ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ more...

Amhara regional health bureau

የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና የሕብረተሰቡን  የጤና ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል ረገድ ከጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር በቅንጅት በመስራት ርህሩህ፣ተገልጋይ አክባሪ እና ሙያዊ ስነ ምግባር የተላበሱ የጤና አገልግሎት ሰጪዎች የማፍራት ስራ፤ ለህብረተሰቡ ችግር ፊቺ የሆኑ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ የጤና አገልግሎት በመስጠት ከጤና ኮሌጁ ጋር በቅንጅት በመስራት ሀገራዊ የጤና ተልእኮን ለማሳካት በጋራ ከጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ more...