/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ 21 ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ሐምሌ 16/2014 ዓ.ም. የተማሪዎች የምረቃ በዓል አከናውኗል፡፡የኮሌጁ መመህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ነው የምርቃት ስነስርአቱ የተካሄደው፡፡ የኮሌጁ ምክትል ዲን መምህር ሔኖክ ዲታ ባደረጉት ንግግር በመከላከል ላይ የተመሠረተውን የሀገራችን የጤና ፖሊሲ ከመተግበር አንጻር ኮሌጁ ለሀገራችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን መሆኑን ገልጸዋል።

 

ኮሌጁ በ2014 ዓ.ም በነርሲንግ ፣ በፋርማሲ ፣ በሚድዋይፍ ፣ በላብራቶሪ ፣ በኢንቫይሮመንታል ኸልዝ ፣ በጀነሪክና አፕግሬድ ጤና ኤክስቴንሽን እና በአንስቴዥያ ሙያ በመደበኛ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 726 የጤና ባለሙያዎች አስመርቋል።

የደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

የደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ግንቦት 15/2013 ዓ.ም. የተማሪዎች የምረቃ በዓል አከናውኗል፡፡የኮሌጁ መመህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ነው የምርቃት ስነስርአቱ የተካሄደው፡፡  የኮሌጁ ዲን አቶ ማሙዬ መንገሻ ባደረጉት ንግግር ትምህርት የአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እድገት ለማምጣት የሚረዳ ቁልፍ መሣሪያ በመሆኑ ኮሌጃችንም ይህንን በመረዳት ጥራት ያለው፣ደረጃውን የጠበቀና ውጤት ሊያመጣ የሚችል ሥልጠና በመስጠት ብቃት ያላቸው ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎችን ለማፋራት አላማዬ ብሎ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡

የደ/ብርሃን ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ቀደም ሲል በመለስተኛ ጤና ባለሙያዎች ማሠልጠኛ ት/ቤትነት በ1991 ዓ.ም የተመሠረተ ሲሆን በ1997 ዓ.ም ከክልሉ መንግስትና ከጤና ጥበቃ ቢሮ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ወደ ጤና ኮሌጅነት ያደገ ኮሌጅ ነው፡፡

Page 1 of 3

Federal Ministry of Health

የፌደራል ጤና ጥበቃ ቢሮ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና የሕብረተሰቡን የጤና ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል ከ21 ጤና ሣይንስ ኮሌጆች ጋር በቅንጅት በመስራት ብቁ የጤና ባለሙያዎችን እንዲያፈሩ፤ ለህብረተሰቡ ችግር ፊቺ የሆኑ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ በተለያየ መልኩ ድጋፍ በማድረግና በቅንጅት በመስራት ሀገራዊ የጤና ተልእኮን ለማሳካት ከጤና ሣይንስ ኮሌጆች ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ more...

Amhara regional health bureau

የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና የሕብረተሰቡን  የጤና ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል ረገድ ከጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር በቅንጅት በመስራት ርህሩህ፣ተገልጋይ አክባሪ እና ሙያዊ ስነ ምግባር የተላበሱ የጤና አገልግሎት ሰጪዎች የማፍራት ስራ፤ ለህብረተሰቡ ችግር ፊቺ የሆኑ ጥናትና ምርምርና የማህበረሰብ የጤና አገልግሎት በመስጠት ከጤና ኮሌጁ ጋር በቅንጅት በመስራት ሀገራዊ የጤና ተልእኮን ለማሳካት በጋራ ከጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ more...